Tuesday, March 4, 2014

አስቸኳይ የቤት ስራ ለሁላችንም ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎EthioMuslims‬



የሚከተሉት መረጃዎች ለአስቸኳይ ስራ የሚፈለጉ በመሆናቸው ሁሉም ሙስሊም በእጁ የሚገኙትን መረጃዎች በማካፈል የሚጠበቅበትን ሃላፊነት ሊወጣ ይገባል፡፡

1. አዲስ አበባን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች በየአካባቢያችን ባሉ መስጂዶች የተደረጉ የሰደቃና አንድነት ፕሮግራሞችን ሲዘጋጁ መግቢያ በር ላይ የተሰቀሉ የነበሩ የመስጂዱን ስም እና የደሰቃ ፕሮግራሙን ማስታወቂያ የያዘውን ባነር በፎቶ

2. በተለያዩ አካባቢዎች መንግስት አንድነት እና የሰደቃውን ፕሮግራም ለማጨናፈግ ካደረገው ተግባራት መካከል በፎቶ የተነሱትን በተለይ መንግስት ክልከላ ሲያደርግ ፣ መንገድ ሲዘጋና ድንኳኖችን ሲያፈርስ እና |የመሳሰሉትን የሚያሳዩ ፎቶዎች ፣

3. የሰደቃና አንድነት ፕሮግራሞችን ለማስታወቅ የተበተኑ የጥሪ ወረቀቶች ፣ ደብዳቤዎችና ማስታወቂያዎችን በፎቶ ማሰባሰብ ፣

4. ሀምሌ 6 የነበረውን ክስተት ( ድብደባዎችና ጭፍጨፋዎችን የሚያሳዩ) ፎቶግራፎች ፣

5. የመንግስትን ጣልቃ ገብነት የሚያሳዩ የምስጂድ መታሸግ፣ፕሮግራም እገዳ፣ ዳዕዋ ክልከላ እና የመሳሰሉትን የያዘ ደብዳቤዎች ፈልገን በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ በዘመቻ መልክ ከላይ የተተቀሱትን መረጃዎች አሰበስበን እንድንልካቸው በአላህ ስም እንጠይቃለን ፡፡ ማንኛውም ሙስሊም እነዚህ ከላይ የተጠቀሱትን እና በእጁ የሚገኙትን ፎቶዎች እና ዶክመንቶች ለመሰብሰብ እንዲያመች በቅርብ ለምናገኛቸው የፌስቡክ አክቲቪስቶች እና ከዚህ ቀጥሎ በተገለፁት ኢስላማዊ ፔጆች ላይ በመላክ |የበኩላችንን ሃላፊነት እንወጣ፡፡

በFree Our Heroes፣ Furaat Orgrat፣ ፈስቢር፣ Ethio Bilal Tube፣ FITH RADIO [ፍትህ ሬዲዮ]፣ BBN ቢቢኤን የናንተው ድምፅ፣ እንዲሁም መሰል ፔጆች ላይ ቢላኩ በቀላሉ መሰብሰብ ይቻላል ፡፡
ለምታደርጉት ትብብር ሁሉ አላህ ምንዳችሁን ይክፈላችሁ ድል ለሙስሊሙ !
አላሁ አክበር !

No comments:

Post a Comment