የሒጃብ ዋጋ በኛዋ ኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች እና በአሜሪካ ትምህርት ቤት #EMUS አጃዒብ ነው አንብባችሁ አጋሩ
የአሜሪካ ግዛት በሆነው ሚቺጋን የሚገኘው የ‘ብራይቶን’ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሙስሊም ያልሆኑ ተማሪዎች በትምህርት ክፍለ ጊዜያቸው ለአንድ ቀን ሙሉ ሒጃብ ለብሰው ዋሉ #EMUS
በብራይቶን /Brighton/ ሃይስኩል የሚማሩ ብዛት ያላቸው የሌላ ሃይማኖት ተከታይ ተማሪዎች ና መምህራቸው ባለፈው የታህሳስ ወር ላይ ነበር ላንድ ቀን ሙሉ በምርጫቸው ሒጃብን ለብሰው ማ ሻ አላህ በሚያስብል መልኩ አጊጠውበት የዋሉት:: ይህን ውሳኔ እንዲወስዱ ያደረጋቸው በዕለቱ ስለ ሃይማኖት ና ማንነት ርዕሰ ጉዳይ በነበራቸው ክፍለ ትምህርት የሙስሊም ሴቶችን ያለባበስ ስርዓት ለመማር የታቀደ ስለነበር ነው::
በወቅቱም በጽንሰ ሃሳብ /Theory/ ደረጃ ጉዳዩን ከማውራት ይልቅ ተማሪዎቹ ና መምህሯ ራሳቸውን በቦታው በማስቀመጥ እንደ ሙስሊም ሴት ሒጃብ መልበስ የሚኖረውን ስሜት በራሳቸው ላይ በማንጸባረቅ ትምህርቱን ወደራሳቸው ህይዎት ለማዋሃድ የተጠቀሙበት ስልት ነው:: ጉዳዩም ሙስሊም ሴቶች እንደ ሙስሊምነታቸው ሂጃብን በመልበስ ማንነታቸውን /Muslim Identity/ እንዴት እንደሚያንጸባርቁ ለመገንዘብ አጋዥ ነበር:: በተያያዥነት ሒጃብ እንደ የአንድ ማህበረሰብ ግብረ ገባዊ መገለጫነት ሲቀመጥ ለጨዋ ስነ ምግባር ያለውን ሚና በተግባር የሞከሩበትም ነበር::
ከየትኛውም የእድሜ ደረጃ ይልቅ በወጣትነት የሃይስኩል ዕድሜ ላይ የምንለብሰውን ነገር የመወሰን ምርጫችን ራሳችንን እንዴት እንደምናይ /ማንነታችንን በመገንባት ና በማንጸባረቅ/ በእጅጉ ይወስነዋል:: ተማሪዎች በዚህ ሂደት የሙስሊሙን ማህበረሰብ ሃይማኖት : ባህል ና ማንነትን በመረዳት ሂደት ተግባራዊ የህይዎት ልምድ ና ትምህርት ቀስመውበታል::
በዚህ ምንም ሙስሊም ተማሪ በሌለበት እና አንድ ብዙም ሃይማኖተኛ ያልሆነች ሙስሊም መምህርት ባለችበት ሁኔታ ሂጃብን አድርጎ የመማር ማስተማር ድርጊት መከናወኑ የተወሰኑ አስተያየት ሰጪዎችን ባለባቸው የኢስላም ና ሙስሊሞች ላይ ጥላቻ ሳቢያ ሲያናጫቸው ሰንብቷል:: አንዳንዶቹ ይህን ዜና ባሰራጩ የዜና ማሰራጫ ድህረ ገጾች ላይም ተማሪዎቹ ና መምህሯ ሂጃብ መልበስ 'ለምን ሲባል ሞከሯት : እንዴትስ ተደፈርን' በሚል ዘራፍ ሊሉም ሞክረዋል::
ይህም ድርጊታቸው ከሃገራችን የትምህርት ተቋማት አመራሮች ና ፖሊሲ አውጭ የመንግስት አካላት ጋር አንድ ያደርጋቸዋል:: በሃገራችን የትምህርት ተቋማት እየተማሩ ባሉ እህቶቻችን ሂጃብ መልበስ አይናቸው የደም እንባ ሲያነባ እያስተዋልነው ያለ ጉዳይ ነውና::
ይህ በንዲህ እያለ በሃገራችን ባሉ ሁለተኛ ደረጃ ና የመሰናዶ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ዩኒቨርስቲ ና ኮሌጆች ያሉ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ሃይማኖታችን ግዴታ ያደረገብንን የሒጃብ ና ሰላት ድንጋጌዎች በትምህርት ተቋማት መተግበር እርም ሊያደርጉ በየጊዜው ደፋ ቀና እያሉ ነው:: እኛ ግን መቸም አንሰማቸውም : አንቀበላቸውም : መስሚያ ጆሮ የለንም:: የማነታችን ና ህልውናችን አካል በሆኑ በሃይማኖታዊ ግዴታወቻችን ላይ አንደራደርም:: ህገ መንግስታዊ የሰብዓዊ መብታችን ነው:: ከነማንነታችን የዜግነት ሃይማኖት ና ብሄር ሙሉ ስብዕናችን መብታችን ተከብሮ እንማራለን::
በዚህም መንግስት ና በየደረጃው ያሉ ጀሌዎቹ መሰረታዊ የህገ መንግስት መርሆችን በመጻረር የተማሪዎችን የማመን : እንዲሁም በግል ና በቡድን ሃይማኖታቸውን የመተግበር ና የማንጸባረቅ መብታቸውን ተጋፍቷል:: ከመጋፋት አልፎ በፍጹም ሊነጠቅ ና ሊገፈፍ የማይችል የመማር ሰብዓዊ መብታችንን በሃይል ሲገድብ እያየን ነው:: መንግስት ከዚህ መሰል ድርጊቱ መታቀብ ሊኖርበት ይገባል::
ከዚህ ና መሰል የሌሎች ሃገሮች ተሞክሮዎችም ልምድን በበቂ ቀስሞ : አስተሳሰቡን ና ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ና ተማሪዎች ያለውን አመለካት በመግራት : የሙስሊሙን መብት ያከበረ : በልማቱም ተሳታፊና ተጠቃሚነቱን ያረጋገጠ ፖሊሲ ና መመሪያ አርቅቆ በማስፈጸም አብሮን ሊሰራ ይገባል::
እኛ ወጣቶች ወደ ጎልማሳነት የእድሜ ገደብ ስንሻገር ባንድ ጠባብ ሂደት ውስጥ እናልፋለን:: ይህም በአቻዎቻችን ባህሪ ና አመለካከት ተገዢ በመሆን በተጽዕኗቸው ስር መውደቅ ወይንም የራሳችንን የጠራ የግል አቋም በማንጸባረቅ ማንነታችንን መገንባት::
ከዚህ አንጻር እኛ እንደሙስሊም ሃይማኖታችን ዲነል ኢስላም ያዘዘንን ማንኛውም ነገር በራሳችን ላይ ከመፈጸም ሊያግደን የሚገባ ተጽዕኖ ሊኖር አይገባም:: ሙስሊምነታችን ኩራታችን : እስልምና ጌጣችን : ሱና ሃብታችን : ሒጃብ ማንነታችን :ሰላት ህልውናችን ነው::
#የተማሪዎችጉዳይ #የትውልድጉዳይነውና #የህዝብጉዳይነው
አላህ በቂያችን ነው! ድልም ከአላህ እንጅ ከሌላ አይደለም!
አላሁ አክበር!
ይህን መልዕክት ሼር በማድረግ ግዴታዎን ይወጡ፡፡
**************
ወደዚህ ፔጅ ወዳጅ ዘመዶችዎን በፌስቡክ በመጋበዝ የበኩልዎን ይወጡ : መረጃዎችንም ሼር (SHARE), ላይክ (LIKE) እና ታግ (TAG) በማድረግ እናዳርስ
የአሜሪካ ግዛት በሆነው ሚቺጋን የሚገኘው የ‘ብራይቶን’ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሙስሊም ያልሆኑ ተማሪዎች በትምህርት ክፍለ ጊዜያቸው ለአንድ ቀን ሙሉ ሒጃብ ለብሰው ዋሉ #EMUS
በብራይቶን /Brighton/ ሃይስኩል የሚማሩ ብዛት ያላቸው የሌላ ሃይማኖት ተከታይ ተማሪዎች ና መምህራቸው ባለፈው የታህሳስ ወር ላይ ነበር ላንድ ቀን ሙሉ በምርጫቸው ሒጃብን ለብሰው ማ ሻ አላህ በሚያስብል መልኩ አጊጠውበት የዋሉት:: ይህን ውሳኔ እንዲወስዱ ያደረጋቸው በዕለቱ ስለ ሃይማኖት ና ማንነት ርዕሰ ጉዳይ በነበራቸው ክፍለ ትምህርት የሙስሊም ሴቶችን ያለባበስ ስርዓት ለመማር የታቀደ ስለነበር ነው::
በወቅቱም በጽንሰ ሃሳብ /Theory/ ደረጃ ጉዳዩን ከማውራት ይልቅ ተማሪዎቹ ና መምህሯ ራሳቸውን በቦታው በማስቀመጥ እንደ ሙስሊም ሴት ሒጃብ መልበስ የሚኖረውን ስሜት በራሳቸው ላይ በማንጸባረቅ ትምህርቱን ወደራሳቸው ህይዎት ለማዋሃድ የተጠቀሙበት ስልት ነው:: ጉዳዩም ሙስሊም ሴቶች እንደ ሙስሊምነታቸው ሂጃብን በመልበስ ማንነታቸውን /Muslim Identity/ እንዴት እንደሚያንጸባርቁ ለመገንዘብ አጋዥ ነበር:: በተያያዥነት ሒጃብ እንደ የአንድ ማህበረሰብ ግብረ ገባዊ መገለጫነት ሲቀመጥ ለጨዋ ስነ ምግባር ያለውን ሚና በተግባር የሞከሩበትም ነበር::
ከየትኛውም የእድሜ ደረጃ ይልቅ በወጣትነት የሃይስኩል ዕድሜ ላይ የምንለብሰውን ነገር የመወሰን ምርጫችን ራሳችንን እንዴት እንደምናይ /ማንነታችንን በመገንባት ና በማንጸባረቅ/ በእጅጉ ይወስነዋል:: ተማሪዎች በዚህ ሂደት የሙስሊሙን ማህበረሰብ ሃይማኖት : ባህል ና ማንነትን በመረዳት ሂደት ተግባራዊ የህይዎት ልምድ ና ትምህርት ቀስመውበታል::
በዚህ ምንም ሙስሊም ተማሪ በሌለበት እና አንድ ብዙም ሃይማኖተኛ ያልሆነች ሙስሊም መምህርት ባለችበት ሁኔታ ሂጃብን አድርጎ የመማር ማስተማር ድርጊት መከናወኑ የተወሰኑ አስተያየት ሰጪዎችን ባለባቸው የኢስላም ና ሙስሊሞች ላይ ጥላቻ ሳቢያ ሲያናጫቸው ሰንብቷል:: አንዳንዶቹ ይህን ዜና ባሰራጩ የዜና ማሰራጫ ድህረ ገጾች ላይም ተማሪዎቹ ና መምህሯ ሂጃብ መልበስ 'ለምን ሲባል ሞከሯት : እንዴትስ ተደፈርን' በሚል ዘራፍ ሊሉም ሞክረዋል::
ይህም ድርጊታቸው ከሃገራችን የትምህርት ተቋማት አመራሮች ና ፖሊሲ አውጭ የመንግስት አካላት ጋር አንድ ያደርጋቸዋል:: በሃገራችን የትምህርት ተቋማት እየተማሩ ባሉ እህቶቻችን ሂጃብ መልበስ አይናቸው የደም እንባ ሲያነባ እያስተዋልነው ያለ ጉዳይ ነውና::
ይህ በንዲህ እያለ በሃገራችን ባሉ ሁለተኛ ደረጃ ና የመሰናዶ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ዩኒቨርስቲ ና ኮሌጆች ያሉ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ሃይማኖታችን ግዴታ ያደረገብንን የሒጃብ ና ሰላት ድንጋጌዎች በትምህርት ተቋማት መተግበር እርም ሊያደርጉ በየጊዜው ደፋ ቀና እያሉ ነው:: እኛ ግን መቸም አንሰማቸውም : አንቀበላቸውም : መስሚያ ጆሮ የለንም:: የማነታችን ና ህልውናችን አካል በሆኑ በሃይማኖታዊ ግዴታወቻችን ላይ አንደራደርም:: ህገ መንግስታዊ የሰብዓዊ መብታችን ነው:: ከነማንነታችን የዜግነት ሃይማኖት ና ብሄር ሙሉ ስብዕናችን መብታችን ተከብሮ እንማራለን::
በዚህም መንግስት ና በየደረጃው ያሉ ጀሌዎቹ መሰረታዊ የህገ መንግስት መርሆችን በመጻረር የተማሪዎችን የማመን : እንዲሁም በግል ና በቡድን ሃይማኖታቸውን የመተግበር ና የማንጸባረቅ መብታቸውን ተጋፍቷል:: ከመጋፋት አልፎ በፍጹም ሊነጠቅ ና ሊገፈፍ የማይችል የመማር ሰብዓዊ መብታችንን በሃይል ሲገድብ እያየን ነው:: መንግስት ከዚህ መሰል ድርጊቱ መታቀብ ሊኖርበት ይገባል::
ከዚህ ና መሰል የሌሎች ሃገሮች ተሞክሮዎችም ልምድን በበቂ ቀስሞ : አስተሳሰቡን ና ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ና ተማሪዎች ያለውን አመለካት በመግራት : የሙስሊሙን መብት ያከበረ : በልማቱም ተሳታፊና ተጠቃሚነቱን ያረጋገጠ ፖሊሲ ና መመሪያ አርቅቆ በማስፈጸም አብሮን ሊሰራ ይገባል::
እኛ ወጣቶች ወደ ጎልማሳነት የእድሜ ገደብ ስንሻገር ባንድ ጠባብ ሂደት ውስጥ እናልፋለን:: ይህም በአቻዎቻችን ባህሪ ና አመለካከት ተገዢ በመሆን በተጽዕኗቸው ስር መውደቅ ወይንም የራሳችንን የጠራ የግል አቋም በማንጸባረቅ ማንነታችንን መገንባት::
ከዚህ አንጻር እኛ እንደሙስሊም ሃይማኖታችን ዲነል ኢስላም ያዘዘንን ማንኛውም ነገር በራሳችን ላይ ከመፈጸም ሊያግደን የሚገባ ተጽዕኖ ሊኖር አይገባም:: ሙስሊምነታችን ኩራታችን : እስልምና ጌጣችን : ሱና ሃብታችን : ሒጃብ ማንነታችን :ሰላት ህልውናችን ነው::
#የተማሪዎችጉዳይ #የትውልድጉዳይነውና #የህዝብጉዳይነው
አላህ በቂያችን ነው! ድልም ከአላህ እንጅ ከሌላ አይደለም!
አላሁ አክበር!
ይህን መልዕክት ሼር በማድረግ ግዴታዎን ይወጡ፡፡
**************
ወደዚህ ፔጅ ወዳጅ ዘመዶችዎን በፌስቡክ በመጋበዝ የበኩልዎን ይወጡ : መረጃዎችንም ሼር (SHARE), ላይክ (LIKE) እና ታግ (TAG) በማድረግ እናዳርስ
No comments:
Post a Comment