Tuesday, March 4, 2014

‹‹730 ቀናት ለሃይማኖት ነፃነት›› የተሰኘው አዲሱ ዘጋቢ ፊልም ይፋ ሆነ!

ድምፃችን ይሰማ
‪#‎EthioMuslims‬ ‪#‎730DaysforReligiousFreedom‬
‹‹730 ቀናት ለሃይማኖት ነፃነት›› የተሰኘው አዲሱ ዘጋቢ ፊልም ይፋ ሆነ!
ሰኞ የካቲት 24/2006

የትግላችንን ሁለተኛ አመት ለማሰብ ከሳምንታት በፊት ለ15 ቀናት ባካሄድነው የዘመቻ ፕሮግራም ታቅደው ከነበሩ ስራዎች አንዱ የሁለቱን አመት ትግላችንን በመጠኑ የሚያስቃኝ ዘጋቢ ፊልም ማዘጋጀት እንደነበረ ይታወሳል፡፡ ከሰሞኑም ፊልሙ በቅርብ ቀን ይፋ የሚሆን መሆኑ ተገልጾ የፕሮቫ ማስታወቂያ መለቀቁ አይዘነጋም፡፡

እስካሁን በተለያዩ ምክንያቶች በመዘግየቱ ይቅርታ እየጠየቅን ‹‹730 ቀናት ለሃይማኖት ነፃነት›› የተሰኘው ዘጋቢ ፊልም በዛሬው እለት ይፋ መሆኑን በደስታ እንገልጻለን! እንደተለመደው ፊልሙን ላልደረሳቸው እንዲደርስ የማድረጉን ሃላፊነት እንደህዝብ ተረባርበን መሸከም እንደሚኖርብን ሳናስታውስ አናልፍም!

የዘጋቢ ፊልሙ ሊንክ፡-

http://www.youtube.com/watch?v=heZkMThP2hQ&feature=youtu.be

ትግላችን እስከድል ደጃፍ ድረስ ይቀጥላል!
ድምጻችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

No comments:

Post a Comment