MARCH 23, 2014
ዛሬ ማለዳ 12:55 ላይ ከካራ ቆሬ ወደ ለገሃር ሲጓዝ የነበረ የከተማ አውቶብስ 15 ሜትር ጥልቀት ካለው ድልድይ ውስጥ ገብቶ ስምንት ሰዎች ህይወታቸው አለፈ።
አደጋው የደረሰው ከካራ ቆሬ ወደ ለገሃር ቁጥራቸው በትክክል የማይታወቅ ተሳፋሪዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረው 36 ቁጥር የከተማ አውቶብስ ፥ ዘነበወርቅ አለርት ሆስፒታል ፊት ለፊት ባለው ረዥም ድልድይ ውስጥ በመግባቱ ነው።

በአደጋው እስካሁን አንድ እግረኛን ጨምሮ አራት ወንድ እና አራት ሴት ተሳፋሪዎች ህይዎታቸው ያለፈ ሲሆን 46 የሚሆኑት ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
የአውቶብሱ አሽከርካሪና ትኬት ቆራጭ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸው በህይወት መትረፋቸው ታውቋል።
ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ተሳፋሪዎች በጥቁር አንበሳና ጳውሎስ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።
የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ ሲሆን አውቶብሱን ከገባበት ገደል ለማውጣትም ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው።
አደጋው የደረሰው ከካራ ቆሬ ወደ ለገሃር ቁጥራቸው በትክክል የማይታወቅ ተሳፋሪዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረው 36 ቁጥር የከተማ አውቶብስ ፥ ዘነበወርቅ አለርት ሆስፒታል ፊት ለፊት ባለው ረዥም ድልድይ ውስጥ በመግባቱ ነው።

በአደጋው እስካሁን አንድ እግረኛን ጨምሮ አራት ወንድ እና አራት ሴት ተሳፋሪዎች ህይዎታቸው ያለፈ ሲሆን 46 የሚሆኑት ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
የአውቶብሱ አሽከርካሪና ትኬት ቆራጭ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸው በህይወት መትረፋቸው ታውቋል።
ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ተሳፋሪዎች በጥቁር አንበሳና ጳውሎስ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።
የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ ሲሆን አውቶብሱን ከገባበት ገደል ለማውጣትም ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው።
No comments:
Post a Comment