Tuesday, December 25, 2012

ESAT Meade Esat Ethiopia Dec 24 2012

WHO IS TAMAGN BEYENE  ?

ESAT Daily News Amsterdam 25 December 2012 Ethiopia

የኢሳት ገቢ ማሰባሰቢያ የተሳካ እና ውጤታማ ለማድረግ በ አንድነት ተነስተናል 
ሰላም ወገኖች
እኛ በኖርዎይ የምንገኝ የኢትዮጵያ ስደተኞች ሃገራችን የሚገኘውን ዘረኛ ፣ አፋኝ እና አምባገነን መንግስት በመቃዎም ሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች እያደረግን እንገኛለን ። ከነዚህ እንቅስቃሴዎች መካከል አንዱ የኢትዮጵያን ህዝብ እውነተኛ የሆነ መረጃ እንዲያገኝ ፤ በሃገር ወዳድ የኢትዮጵያ ዜጎች የተቋቋመውን ኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥንን(ኢሳት) መርዳት ነው ።
እንደምናውቀው ተራራውን አንቀጠቀጠን የሚሉትን የማፊያ ቡድን ወያኔን ፤ ኢሳት እውነት ለኢትዮጵያን ህዝብ በማቀበል ብቻ እያንቀጠቀጣቸው ይገኛል ። ኢሳት የኢትዮጵያን ብቸኛ ህዝብ አይን እና ጆሮ ብቸኛ ሳይሆን በተግባርም አንደበት ስለሆነ Feb 10-2013 በ ኖርዎይ ዋና ከተማ በኦስሎ ይካሄዳል ። በዚህ ቀን ሃገር ወዳድ ወንድማችን ታማኙ አርቲስት ታማኝ በየነ ተጋባዥ እንግዳችን ነው ። ለኢሳት ፣ ለአርቲስት ታማኝ በየነ እንዲሁም ለኢትዮጵያን ህዝብ ክብር ስንል በስደት የምንኖርበት ሃገር የሚደረገውን የገቢ ማሰባሰቢያ የተሳካ እና ውጤታማ ለማድረግ በ አንድነት ተነስተናል ።
በዚህ አጋጣሚ በኖርዎይ የምትገኙ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያ ወዳጆች በዚህ ዝግጅት በመገኘት ኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥንን (ኢሳት) ለሚደረገው የገቢ ማሰባሰቢያ የራስዎን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ በክብር ጋብዘንዎታል ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!
ሞት ለውያኔ እና ሆድ አደሮች !!!


THERE WILL BE FUNDRAISING CAMPAIGN IN OSLO, NORWAY FEBRUARY 10 2012 WITH A FAMOUS ARTIST AND ACTIVIST TAMAGNE BEYENE. 

THERE WILL BE A MEETING FROM 12.00 OKLOCK, 
MUSIC PROGRAM, ETHIOPIAN TRADITIONAL AND MODERN MUSIC WITH A TRADITIONAL ETHIOPIAN DANSERS AND FOOD. 

THE ENTRANCE IS 200 KR. 

COME ENJOY AND HELP ESAT THE ONLY WAY TO BREAK THE SILENCE IN ETHIOPIA.

Adress. Halvardshjemmet 3rd buss stop from Oslo S, by buss no. 32. 

Thursday, December 20, 2012

የኢሳት ገቢ ማሰባሰቢያ የተሳካ እና ውጤታማ ለማድረግ በ አንድነት ተነስተናል


ሰላም ወገኖች
እኛ  በኖርዎይ የምንገኝ የኢትዮጵያ ስደተኞች ሃገራችን የሚገኘውን ዘረኛ ፣ አፋኝ እና አምባገነን መንግስት  በመቃዎም  ሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች እያደረግን እንገኛለን ። ከነዚህ እንቅስቃሴዎች መካከል አንዱ የኢትዮጵያን  ህዝብ እውነተኛ የሆነ መረጃ እንዲያገኝ ፤ በሃገር ወዳድ የኢትዮጵያ ዜጎች የተቋቋመውን  ኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥንን(ኢሳት)  መርዳት ነው ።


እንደምናውቀው ተራራውን አንቀጠቀጠን የሚሉትን የማፊያ ቡድን ወያኔን ፤ ኢሳት እውነት ለኢትዮጵያን  ህዝብ በማቀበል ብቻ እያንቀጠቀጣቸው ይገኛል ። ኢሳት የኢትዮጵያን  ብቸኛ ህዝብ አይን እና ጆሮ  ብቸኛ ሳይሆን በተግባርም አንደበት ስለሆነ  Feb 10-2013  በ ኖርዎይ ዋና ከተማ በኦስሎ  ይካሄዳል ። በዚህ ቀን ሃገር ወዳድ ወንድማችን ታማኙ  አርቲስት ታማኝ በየነ  ተጋባዥ እንግዳችን  ነው ። ለኢሳት ፣ ለአርቲስት ታማኝ በየነ  እንዲሁም ለኢትዮጵያን ህዝብ ክብር ስንል  በስደት የምንኖርበት ሃገር የሚደረገውን የገቢ ማሰባሰቢያ የተሳካ  እና ውጤታማ ለማድረግ በ አንድነት ተነስተናል ።

 በዚህ አጋጣሚ  በኖርዎይ የምትገኙ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያ ወዳጆች በዚህ ዝግጅት በመገኘት  ኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥንን (ኢሳት) ለሚደረገው የገቢ ማሰባሰቢያ የራስዎን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ በክብር ጋብዘንዎታል ።


ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ  !!!
ሞት ለውያኔ እና ሆድ አደሮች !!!

Wednesday, December 19, 2012

መስፍን ኢንጂነሪንግ ኩባንያ የ2.6 ቢሊዮን ብር ኮንትራት ተሰጠው


ኢሳት ዜና:-ባለቤትነቱ የሕወሀት የሆነው መስፍን ኢንጂነሪንግ ኩባንያ ከሶስት የስኳር ፋብሪካዎች የ2.6 ቢሊዮን ብር ኮንትራት እንደወሰደ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዘገበ።
ከተቋቋመ 19 አመት የሞላውና የትግራይ መልሶ ማቋቋም ኢንዳውመንት ፈንድ የተሰኘው ግዙፍ ድርጅት አካል የሆነው መስፍን ኢንጂነሪንግ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚገነቡ 3 ስኳር ፋብሪካዎች የሚሆኑ የማፍሊያ ቤቶችን (ቦይሊንግ ሀውሶች) ለመገንባት ነው የ2.6 ቢሊዮን ብሩን ኮንትራት የወሰደው።
የመስፍን ኢንጂነሪንግ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ አማኑኤል ገብረኪዳን ለኢቲቪ እንደገለጹት፤ ፋብሪካው ከ2 ዓመት በሁዋላ አመታዊ ትርፉን ወደ 600 ሚሊዮን ብር ለማሳደግ እየሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።
ከዚህም በተጨማሪ መስፍን ኢንጂነሪንግ በቦሌ ዞን በ35 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ይገነባል የተባለውን የኢንዱስትሪ ዞን ኮንትራት ወስዶ እየገነባ እንደሆነ ዜናው ጠቁሟል።
መስፍን ኢንጂነሪንግ ከሶስቱ ቦይሊንግ ሀውሶች በተጨማሪ ለስኳር ፋብሪካዎቹ የሚያገልግሉ ላብራቶሪዎችን የመገንባት ኮንትራትም እንደወሰደ ኢቲቪ ጨምሮ ገልጿል።
የኢትዮጵያ ህግ የፖለቲካ ፓርቲዎች በንግድ ውስጥ እንዳይሰማሩ ቢከለክልም፤ ባለቤትነቱ የሕወሀት የሆነው የትግራይ መልሶ ማቋቋም ኤንዳውመንት ፈንድ፤ በእንግሊዘኛው ምህጻረ ቃል ኤፈርት፤ ኢህአዴግ ስልጣን ከያዘ ጊዜ ጀምሮ በኢትዮጵያ በተለያዩ የንግድ ዘርፎች እንደተሰማራና ከሼክ አላሙዲን ቀጥሎ በአገሪቱ ውስጥ በብዙ ቢሊዮን ዶላር የሚቆጠር ቢዝነስ እንደሚያንቀሳቅስ ይታወቃል።
ኤፈርት ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ ከመንግስት በሚያገኘው ፖለቲካዊና ወለድ-የለሽ የብድር አገልግሎት በመታገዝ የመንግስት የግንባታ ፕሮግራሞችን ያለተቀናቃኝ በመወስድ የሌሎች የግል ባለሀብቶችን ስራ እንደሚያቀጭጭ አስተያየት ሰጪዎች ይናራሉ።
ስለትግራይ መልሶ ማቋቀም ኤንዳወውመነንት ፈንድ የተጠየቁ የህወሀት አመራሮች ገንዘቡን በትግሉ ሰዓት ያፈራነው ነው ባለቤትነቱም የትግራይ ህዝብ ነው ሲሉ መልስ የሚሰጡ ሲሆን፤ ድርጅቱ ከተቋቋመ እስካሁን ድረስ ምንም አይነት የውጭ ኦዲት እንፈደማያውቀው የራሱ ህሀወት ባለስልጣናት ይተቻሉ።
ኤፈርት ከመጀመሪያው የድርጅቱ ቦርድ ሊቀመንበር አቶ ስዬ አብርሀ ጊዜ ጀምሮ ከንግድ ባንክ ዋስትና የለሽ የብድር አገልግሎት ያገኝ እንደነበር የሚነገር ሲሆን፤ ከወራት በፊት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተበላሹ ብድሮች በሚል የኤፈርትን እዳዎች መሰረዙን መዘገባችን ይታወሳል።
በአሁኑ ሰዓት የኤፈርት የቦርድ ሊቀመንበር የሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ናቸው።

ESAT DC Daily News December 18 2012